• (+251)462125955
  • SNNPRS, Hwassa Ethiopia

የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት

  • የዳይሬክቶሬቱን ስራዎች በመምራት እና በማስተባበር፣ የኦዲት አሰራሮችን ለማሻሻል የመከናወኑ ጥናቶች፣ የክትትልና ድጋፍ ተግባራትን በመምራትየመንግስት ሃብት ለታለመለት ዓላማ መዋሉን ለማረጋገጥ ነው፡፡
  • የዳይሬክትሬቱን ሥራዎች ያቅዳል፣ ለባለሙያዎች ያከፋፍላል
  • የዳይሬክትሬቱን ለስራ አስፈላጊ የሁኑ ግብዓቶች እንዲሟሉ ያደርጋል
  • የዳይሬክተሩን ስራዎች ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ አዳዲስ የአሰራር ስርዓቶችን ይዘረጋል፤ ስልቶችንም ይነድፋል፡፡
  • የዳይሬክቶሬቱን ስራዎች ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት በቅንጅት ለመስራት የሚያስችሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ይዘረጋል፡፡
  • በዳይሬክቶሬቱ ሥር ያሉ ፈጻሚ ባለሙያዎች አቅማቸው እንዲገነባ ያደርጋል፤
  • የባለሞያውን የስራ አፈጻጸም ይከታተላል፣ ይገመግማል፣ ግብረ መልስ ይሰጣል፣
  • መ/ቤቶች የውስጥ ኦዲት የአሰራር ችግሮች በጥናት እንዲለዩ ያደርጋል፡፡
  • የውስጥ ኦዲትን የሚመለከቱ በባለሙያዎች የሚቀርቡ የፖሊሲ ሃሳቦችን ይገመግማል፤ማሻሻያ በማድረግ ያጠቃልላል፡፡
  • የውስጥ ኦዲት አሠራር በተመለከተ በባለሙያዎች የሚቀርቡ አዳዲስ የአሰራር ስርዓቶች፣ መመሪያዎችንና ማንዋሎችን ይገመግማል፤ማሻሻያ በማድረግ እንዲጸድቅ ያደርጋል፤፤
  • ከውስጥ ኦዲት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን በዓለምና አገር አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን እንዲካሄዱ አሰፈላጊውን ነገር ያመቻቻል፡፡
  • በባለበጀት መ/ቤቶች አሰራሮች ውጤታማ የሆነ የውስጥ ኦዲት አደረጃጀት ለመፍጠር የሚካሄዱ ጥናቶችን በበላይነት ያስተባብራል፤የሚቀርቡ የጥናት ውጤቶችን ይገመግማል፤ማሻሻያ በማድረግ ያጸድቃል፡፡
  • የውስጥ ኦዲት በሥራው ምክንያት የሚደርስበትን ተጽእኖ እንዲጣሩና መፍትሄ እንዲያገኙ ያደርጋል፡፡
  • የውስጥ ኦዲት አሰራርን በተመለከተ የበላይ ኃላፊዎችና ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች የተለያዩ የግንዛቤ ማስጫበቻ ስልጠናዎችና የውይይት መድረኮች እንዲዘጋጁ አስፈላጊውን ነገር ያመቻቻል፡፡
  • ከሙያና ከስልጠና ተቋማት ስልጠናዎችን ለማግኘት የሚያስችሉ ፕሮጀክት እንዲቀረጹ ያደርጋል፤ ስልጠናዎችንም ያፈላልጋል፣
  • የኦዲት እቅድ ዝግጀት እና የስጋት አካባቢዎችን የመለየት የሚደረጉ ጥናቶችን ያስተባብራል፤ በበላይነት ይመራል፡፡
  • በተቋማት የአስተዳደር ሥርዓት /Governance/ እንዲገመገም ያደርጋል፡፡
  • በተለዩት የስጋት አካባቢዎች መስረት የፋይናሻል፣ የሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት እንዲሁም የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት ግምገማ እንዲከናወኑ ያደርጋል፤ሂደቱንም በበላይነት ያስተባብራል፤ይመራል፤
  • በባለሙያዎች የሚቀርቡ የፋይናሻል፣ የሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት እንዲሁም የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት ግምገማ የኦዲት ሪፖርቶች በመገምገም እንዲጠቃለሉ ያደርጋል፡፡
  • በኦዲት መውጫ ስብሰባ ላይ በመገኘት ስብሰባውን ይመራል ያወያያለ፤
  • በውይይቱ ወቅት በተደረሰባቸው ስምምነቶች መሠረት ተዘጋጅቶ የቀረበለትን የኦዲት ሪፖርት ትክክለኛነት አረጋገጥ ያስተላልፋል፤
  • የውስጥ ኦዲት አሠራር በተመለከተ የተዘጋጁ አዳዲስ የአሰራር ስርዓቶችን፣ መመሪያዎችንና ማንዋሎችን በአግባቡ ተግባራዊ መደረጋቸውን ክትትልና ቁጥጥር መደረጉን ይከታተላል፤ይቆጣጠራል፤
  • ከመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚቀርቡ የውስጥ ኦዲት እቅዶችንና ሪፖርቶችእንዲገመገሙ በማድረግ የማሻሻያ ሃሳቦችንለተቋማት ይልካል፡፡
  • መ/ቤቶች ኦዲቱ ሲከናወን በተዘጋጀው የኦዲት ፕሮግራም መሰረት ሥራው እየተከናወነ መሆኑን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል፤
  • በውስጥና በውጪ ኦዲተሮች በተሰጡ የኦዲት አስተያየትና ማሻሻያ ሃሳቦች መሰረት የተወሰዱ የእርምት እርምጃዎች በአግባቡ መገምገሙንይከታተላል፤ይቆጣጠራል፡፡
  • በባለሙያዎች የሚቀርቡ የመ/ቤቶች የተጠቃለለ የውስጥ ኦዲት ሪፖርት ይገመግማል፤ማሻሻያ በማድረግና በማጸደቅ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት እንዲላክ ያደርጋል፡፡
  • በመ/ቤቶች አንኳር የኦዲት ግኝቶች ሪፖርት ላይ ተመስርቶ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የተሰጠ አመራር ተፈጻሚነትን ይከታተላል፤ ይቆጣጠራል፤
  • የውስጥ ኦዲት ክትትልና ድጋፍ በተመለከተ ለባለሙያዎች የተሰጡ ስልጠናዎች የመጡትን ለውጥ ይከታተላል፤ይገመግማል፣
  • የዳይሬክቶሬቱን ዓመታዊ፣ የሩብ ዓመት፣ የግማሽ ዓመት፣ የዘጠኝ ዓመት ዕቅድና የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቶችን ለቅርብ ኃላፊና ለቢሮ በተቀመጠዉ የጊዜ ገደብ ያቀርባል፣
  • በዳይሬክቶሬቱ የሰዉ ኃይል በመዋቅሩ መሠረት እንዲሟላ ያደርጋል፣
  • በዳይሬክቴሩ የሚያስፈልጉ የሥራ ቁሳቁሶች እንዲሟላ ያደርጋል፣
  • ስራውን ለማስፈፀም የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራቶችን ይፈጽማል፡፡