• (+251)462125955
  • SNNPRS, Hwassa Ethiopia

የሥነ-ህዝብ ትምህርትና ቅስቀሳ

  • የተለያዩ  የሥነ-ህዝብ  ደንብ፣ መመሪያ፣  የሥልጠና እና ስትራቴጂ  ሰነድ  ማዘጋጀትና ማሻሻል፤
  • በሥነ-ህዝብ ጉዳዮች የማህበረሰቡንና አመራር አካላትን ግንዛቤ ለማጐልበት የሚያስችሉ የትምህርትና ቅስቀሳ ሥራዎችን ለማስፈጸም የሚረዱ  የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት አፈጻጸማቸውን መገምገም፣  ድጋፍና ክትትል ማድረግ፤
  • በሁሉም አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤቶች የሥነ-ሕዝብ ክበባትን በማቋቋም፣ ውጤታማነታቸውን በመከታተል፣ በተለያዩ ቁሳቁሶች በመደገፍ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድርን ማስተባበር፤   
  • የተለያዩ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት ለአመራሩ (ለውሳኔ ሰጪ አካላት) እና ለህብረተሰቡ በሥነ-ሕዝብ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ በመፍጠር ለሥነ-ህዝብ ችግሮች የመፍትሄ ባለቤት እንዲሆኑ ማስቻል፤
  • የማህበረሰብ ውይይቶችን በማካሄድ የሥነ-ሕዝብ ችግሮችን  የመከላከልና የመፍታት ሥራዎችን ማቀድ፣  ማስተባበርና መምራት፤
  • የሥነ-ህዝብ ቀን በዓል አከባበር ሥራን ማቀድ፣ መምራት፣ ማስተባበር፤
  • የሥነ-ሕዝብ መልዕክቶችን የያዙ የተለያዩ መጽሄቶች፣ብሮሸሮች፣ቡክሌቶች እና የመሳሰሉትን አዘጋጅቶ በማሳተም ለህብረተሰቡ ማሰራጨት፤
  • በሥነ-ሕዝብ ችግሮች ዙሪያ ተከታታይ ት/ት ሰጪ መልዕክቶችን /ስክሪፕት/ በማዘጋጀት በሬዲዮ እንዲተላለፍ ማድረግ፤