• (+251)462125955
  • SNNPRS, Hwassa Ethiopia

የማክሮ ኢኮኖሚ ዕቅድ ዝግጅት ክትትል ግምገማ ዘርፍ

  1. የክልሉን የረጅም፣ የመካከለኛና የአጭር ጊዜ ዕቅድ ያዘጋጃል፤ አፈፃፀማቸውን ይከታተላል፤ይገመግማል፤ ሪፖርት በማዘጋጀት ለሚመለከታቸው አካላት ያቀርባል፤
  2. የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቅፍ ያዘጋጃል፤ ለመስተዳድር ምክር ቤት አቅርቦ ያስፀድቃል፤
  3. የክልሉን መንግሥት የካፒታል ፕሮጀክቶች የአዋጭነት ጥናት ያካሂዳል፤ ይገመግማል፤ያስፀድቃል፤
  4. በክልሉ የታችኛውን የአስተዳደር ዕርከን ዓመታዊ የሀብት ማከፋፈያ ቀመር ያዘጋጅል፣ለክልሉ ምክር ቤት እንዲጸድቅ ያቀርባል፣
  5. የክልሉን የካፒታል ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ክትትልና ግምገማ ያደርጋል፤ ወቅታዊ ሪፖርት በማዘጋጀት አግባብነት ላላቸው አካላት ያቀርባል፣
  6. የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ አፈፃፀም ጥናት ያካሂዳል፤
  7. የክልሉን የልማት ክፍተት እና የመልማት አቅም ጥናት ያደርጋል፤
  8. የክልሉን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ገፅታ ጥናት ያደርጋል፣
  9. የክልሉን የመካከለኛ ጊዜ የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቀፍ ያዘጋጃል፤ ያስፀድቃል፤
  10. የክልሉን ዓመታዊ የሀብት ግመታ ሰነድ ያዘጋጃል፤ ለክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በማቅረብ ያስፀድቃል፤
  11. ዓላማውን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል፡፡